ባለፉት ግዜያት “በወርድ ፕሬስ” ነፃ የብሎግ አድራሻ በመጠቀም እንገናኝ እንደነበረ ይታወቃል። አሁኑ ግን በአንድ ፃድቅ ቸሮታ “ዶሜን” ስለተገዛልን  http://www.abetokichaw.com  በሚለው ድረ ገፅ ላይ የተለመዱ ጨዋታዎቻችንን እና መረጃዎችን የምንቀባበልበት አድራሻ አበጅተናል።

ታድያ ለወትሮው በዚህች “በወርድ ፕሬስ ብሎግ” ተመዝግባችሁ በየኢሜላችሁ ስትከታተሉኝ የነበረ ወዳጆች “የት ጠፋህ?” ብላችሁ መልዕክት ሰዳችሁልኝ ባይ ግዜ አዲሱ አድራሻችንን በብሎጋችን ላይ አለመናገሬ ትዝ አለኝ! (ሞት ይርሳኝ… “ጠላትህ” እንዳይሉ ችግር የለም እኔኑ ይርሳኝ! ባይሆን “አብሮይርሳን” ማለት ነው)

አዲሳባ ያላችሁ ወዳጆች  https://www.abetokichaw.com/ በሚል ብትገቡ የሚቻላችሁ ይመስለኛል።

አብሮነታችንን ያጠንክርልን!

About abetokichaw

ራሱን አቤ ቶኪቻው እያለ የሚጠራ አንድ ግለሰብ በአዲሳባ ከተማ ይኖር ነበረ። በአዲሳባ ከተማ በሚኖርበት ግዜ የመንግስትን ያልተስተካከለ አስራር ሲያሽሟጥጥ መንግስት ተቀየመው። ምን መቀየም ብቻ… ከሀገር እንዲሰደድ ሁሉ አደረገው እንጂ! ይህ ግለሰብ… ከዚህ በፊት ሁለት ሽሙጣዊ መፅሐፍትን ያሳተመ ሲሆን “የአቤ ቶኪቻው ሽሙጦች” እና “ስላቆች” ይሰኛሉ። አሁንም ቢሆን የማይሆን ነገር ካየሁ ከማሽሟጠጥ አልመለስም የሚለው ይህ ስደተኛ… እነሆ በዚህ ብሎግ ላይ ደግሞ በሽሙጥ የአፃፃፍ ብልሃት ቢያንስ በሳምንት አንድ ግዜ ልከሰት ብሎ “ሀ” ብሏል።

2 responses »

  1. Tikidem says:

    አቤ እነደምነህ ፣ የቀየርከው ብሎግ አይከፈትም የበፊቱ ግን ማለትም http://www.abetokicaw.wordpress.com የሚለው ይከፈታል ለምን በሱ አትጠቀምም ፡፡ ይሄንን ለመፃፍ አልፈለኩም ይዘጉታል በሚል ግን ምንም ማድረግ አይቻልም ፣ ወይም ለምን በሁለቱም ፖስት አታደርግም ፡፡

    • በለው! says:

      መልካም ነው በሁለቱም ለመጠቀም ወይንም ያንንም ቢሆን ተለየ ሙከራ(ፍተሻ) ይደረግ ሐሳባችንን ስለማግኘትህ ጠቁም በለው!

Leave a comment