ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር፤ እንግዲህ ጠቅላይ ሚኒስትርነት ጣጣው ይሄው ነው። እያንዳንዷ ጥቃቅን ጉዳይዎ ሁላ ለአደባባይ ትበቃለች። ባለፈው ጊዜ የጠቅላይ ሚኒስትሩን ደሞዝ ልክ የሰማን ሰሞን፤ ፕሮፌሰር መስፍን በፃፉት አንድ መጣጥፍ ላይ “ስድስት ሺህ አራት መቶ ብር ላጥ እያደረጉ ማሰር ሰለቸን አይባልም! በአግባቡ ከሆነ ማሰርም መፍታትም ስራዎ ነው!” ብለው ወረፍ አድርገዎት ነበር። እናም መተቸትም መወረፍም የስራዎ አካል ነው ማለት ነው። እናም ቻል ያድርጉት!
ሰሞኑን ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከሰውነት ጎዳና መውጣታቸውን አስመልክቶ በርካታ የኢንተርኔት አሳቢ ወዳጆች አስተያየቶችን ሲሰጡ ተመልክተናል።
ከአስተያቶቹ ውስጥ የተወሰኑትን ለማየት ያክል…
“የማይመቱት ልጅ ሲቆጡት ያለቅሳል” በሚል ርዕስ አንድ ስዕል ተለጥፎ ተመልክተናል። ስዕሉ አቶ መለስ ክስት ብለው በመከራ ለመሳቅ ሲሞክሩ እና አበበ ገላው ከላይ ሆኖ “መለስ ዜናዊ አምባ ገነን ነው… እስክንድር ነጋ እና ሌሎች የፖለቲካ እስረኞች ይፈቱ ነፃነት፣ ነፃነት፣ ነፃነት” ሲል የሚያሳይ ነው።
በነገራችን ላይ እነ እስክንድር ነጋ ላይ ዛሬ ፍርድ ቤቱ የመጨረሻ ውሳኔውን ይሰጣል ተብሎ ይገመታል። በርካቶችም በየ ፌስ ቡካቸው ላይ ንፁሀንን ፍቱልን እነ በርባንን እሰሩልን! እያሉ እወተወቱ ነው… ወደ በርባን ስንመለስ… ብዬ ወደ ስለ ጠቅላይ ሚኒስትሬ የጀመርኩትን ብቀጥል ሌላ ይመስልብኝ ይሆን…!? ስለዚህ እንዳይቀየሙኝ ዝም ብዬ ፌቴን ወደ እርሳቸው አዞራለሁ፤
(ፈጥኖ በደረሰኝ ዜና እነ አስክንድር ነጋ ዳግም ለመጨረሻ ውሳኔ ሰኔ ሃያ እንደተቀጠሩ ሰምቻለሁ! እንኳንም ሰኔ ሰላሳ አልሆነ ሰኔ ሰላሳ የፀብ ቀጠሮ ነው! ብሎኛል መረጃውን አደረሰኝ አሽሟጣጭ!)
ወደ እርሳቸው ስንመለስ…
አንዱ ወዳጃችን ደግሞ “እኔ የምለው ቁጣም እንደ ጂምናዚየም ያከሳ ጀመር እንዴ!?” ብሎ ለጥፏል። ከዚህ ስር ከተመለከትኳቸው አስተያየቶች ውስጥ፤ “ሰውየው እኮ በስብሰባ ፍቅር ጉሉኮሳቸውን ነቃቅለው ነው የተነሱት!” የሚል አስተያየት አይቼ አረ ተዉ ግፍ አትናገሩ ብዬ ሳላበቃ ሌላው ደግሞ “እኚያ ሼክ አላሙዲ አንጠልጥለው ወደ ሀኪም ቤታቸው ቢመልሷቸው ጥሩ ነበር!” የሚል አስተያየት ሰጥቷል።
የሆነ ሆኖ ጠቅላይ ሚኒስትራችን ደንግጠዋል። ድንጋጤውም ህመም ሆኖባቸዋል። ህመሙም አክስሏቸዋል። አክስታቸዋልም። እንግዲህ በዚህ ላይ ደግሞ ውጪ ጉዳይ ሚኒስቴር እና ብሄራዊ ደህንነትና መረጃ ምን አይነት ፊልም እንደሚያዘጋጁ እንጠብቃለን…
በዚህ በቡድን ሃያ ስብሰባ ላይ አባላቶቹ እና ተሳታፊዎቹ በሙሉ ተደርድረው በተነሱት ፎቶግራፍ ላይ ደግሞ አሁንም ከሰው አፍ አይውጡ ያላቸው ጠቅላይ ሚኒስትራችን የመሰወር አደጋ ደርሶባቸዋል። እናም በርካቶች “ጠቅላይ ሚኒስትሩን ያያችሁ አፋልጉን!” እያሉ ማስታወቂያ ለጥፈዋል።
እውነት ግን ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር በቡድን ሃያ ስብሰባ ላይ መካፈልዎን ለማረጋገጥ እኮ በዚህ ፎቶግራፍ ላይ የግድ ልናይዎት ይገባል። አለበለዛ ይሄ በየሰበባ ሰበቡ የሚዞሩትን ነገር… ከቤተሰብ ጋር ያቆራርጦታል። እኛ እንኳ የትም ቢሄዱ ግድየለንም… (የመዘዋወርም ሆነ የመሰወር መብትዎን እናከብራለን!)
አረ እዝች ጋ ዛሬ አወራታልሁ ብዬ ያላሰብኳት አንድ ቀልድ ትዝ አለችኝ የፈጀውን ይፍጅ እና ልንገራችሁ፤
የግንቦት ሃያ በዓል ሲከበር ሁለት ዋና ካድሬዎች በበዓሉ ድግስ ይሄንን ያላበው ቢራ ሲለጉ አምሽተው ሞቅ ብሏቸዋል። ታድያ እንዲህ ሆነን መኪና ከምንነዳ ብለው ለጥንቃቄ ታክሲ ሊይዙ ያነጋግሩ ጀመር! (በቅንፍ እነ አጅሬ ለራሳቸውኮ ጠንቃቆች ናቸው ለኛ ጠንቅ ሆኑብን እንጂ… ልበል ወይስ አልበል…!?)
የሆነው ሆኖ ባለታክሲውን “ሲኤም ሲ ውሰደን እስቲ ዋጋው ስንት ነው!?” ብለው ጠየቁት… ባለታክሲውም ባለጊዜዎች መሆናቸው ገባውና “አምስት መቶ ብር ክፈሉ” አላቸው ይሄኔ በጣም ተበሳጭተው። “እንዴት አምስት መቶ ብር ትለናለህ መቀሌ ውሰደን ብንልህ ስንት ልትለን ነው…!?” ብለው በሞቅታና በብስጭት ጠየቁት። ባለ ታክሲውም “መቀሌ… ሄዳችሁ የማትመለሱ ከሆነ በነፃ እወስዳችኋለሁ!” አላቸው። አሉ። ይህንን ቀልድ ወዳጄ እንደነገረኝ ወድያው በአዕምሮዬ የመጣው የመቀሌ ህዝብስ በምን እዳው ይችላቸዋል…? የሚለው ነበር ስለዚህ ባህር ማሻገር ይሻል ይሆን…!?
እናልዎ ጠቅላይ ሚኒስትሩ የቡድን ሃያ ስብሰባ ብለው ሄደው ነበር። ነገር ግን ተስብሳቢዎቹ ፎቶግራፍ ላይ የሉም ክሳታቸው ይሄንን ያህል እንዳይታዩ አድርጓቸው ነው ወይስ ፎቶግራፍ አንሺው እሳቸው ነበሩ!?
ጠቅላይ ሚኒስተሬ ከወዴት አሉ!?
እርምት አለኝ። “መቀሌ የምትሄዱ ከሆነ በነጻ እወስዳችሗለሁ” ተብሎ ይታረም። ድህረ ገጹ ላይ ያለዉ ግድፈት “የማትሄዱ” የሚል ሲሆን የቀልዱን ትርጉም ለዉጦ ነዉ ያገኘሁትና ይታረም።
አቤ ትክክል ነው:: አማርኛ ሳትችል አራሚ ልሁን አትበል::
“መለስ ዜናዊ አምባ ገነን ነው… እስክንድር ነጋ እና ሌሎች የፖለቲካ እስረኞች ይፈቱ ነፃነት፣ ነፃነት፣ ነፃነት”!!!!!!!
“መለስ ዜናዊ አምባ ገነን ነው… እስክንድር ነጋ እና ሌሎች የፖለቲካ እስረኞች ይፈቱ ነፃነት፣ ነፃነት፣ ነፃነት”!!!!!!!
“መለስ ዜናዊ አምባ ገነን ነው… እስክንድር ነጋ እና ሌሎች የፖለቲካ እስረኞች ይፈቱ ነፃነት፣ ነፃነት፣ ነፃነት”!!!!!!!
aydelem belehe men telaleh!!! chuhetam!!!
አበበ ገላው ያነሳው ፍቶ እንዳይሆን!እሳቸው የከሱት ባልደላው ህዝብ ላይ የደላው መሪ መሆን መልካም አይደለም የሚለውን የተመስገን ደሳለኝን ምክር ሰምተው መሰለኝ!
ኸረ አቤ እንኳን እንደዚ ብለሀቸዉ እሳቸዉን ካላየን እንቅልፍ የሚወስደን አይመስላቸዉም በተለይ ETV ን የወረሩት ሰዎች፤ እንደዚ የምልክ አሽሟጣጭ መሆንህን ረስቼዉ ሳይሆን ከጫካ ለመጡ ሰዎች የሚገባ ስላልመሰለኝ ነዉ::
በጣም ስህተት ነው ቢያንስ አሸብር ተክቷቸው ፎቶውን መነሳት ነበረበት፡፡ ምክንያቱም ‹‹ጠ/ሚንስትሩ ፎቶው ላይ ስለሌሉበት ፕ/ት ኦባማ ፎቶው መደገም አለበት አሉ ሊለን ይችላል›› ኢቲቪ፡፡ ‹‹በየሰበባ ሰበቡ የሚዞሩትን ነገር… ከቤተሰብ ጋር ያቆራርጦታል›› በጣም ተመችታኛለች፡፡ በነገራችን ላይ የወረዳ፣ የዞንና የክልል ባለስልጣናት ሹም ሽር በተሳለጠ ሁኔታ እየተካሄደ ነው ጉልቻ መቀያየር ቢሆንም ቅሉ፡፡
ቻይናዎች አግኝተውልሃል አቢ ከ ኦባማ ካሚራ የተደበቁትን እና ቻይናን ልናመሰግን ይገባል
በአበሻ ምድር ደግ አይበረክትም ፡)
ምናልባት መለስ ከሰውነት ተራ ዎጥተው “መንፈስ” ሆነው ይሆን ፎቶው ላይ የጠፉት? ቂ ቂ ቂ
(…)እናልዎ ጠቅላይ ሚኒስትሩ የቡድን ሃያ ስብሰባ ብለው ሄደው ነበር። ነገር ግን ተስብሳቢዎቹ ፎቶግራፍ ላይ የሉም ክሳታቸው ይሄንን ያህል እንዳይታዩ አድርጓቸው ነው ወይስ ፎቶግራፍ አንሺው እሳቸው ነበሩ!?
*እነኝህ ቡድኖች በተለያየ መልኩ እየተቧደኑ የአለምን ኢኮኖሚ በግሎባላይዜሽን ምህታት በእጃቸው መዳፍ ካስገቡ ሰንብተዋል አሁን የሚገርመው የኢህአዴግን ሊ/መ፣የታጋይ አዜብን ባል፤የሚኒስትሮች ሚ/ር፤የመከላከያው ተከላይ ፤ የምስራቅ አፍሪካ የቀጠናው አተራማሽ ሃላፊ፤የስለላና ማናጋት ተጠሪ፤የአህጉሩ ተመራጭ ምሁር እና ሌሎችንም ለመዘርዘር ሰሌን የማይበቃው ሥልጣን ያላቸውን ደፋር ድንገት በደረሰባቸው የ፸ ከመቶ የአዳራሽ ውስጥ ድንጋጤ በወር ውስጥ ፲፩ ነጥብ የሰውነት መቀነስ ስለደረሰባቸው ለፎቶ መነሳት ከሗላ ግድግዳ አስደግፈው አቁመዋቸው በአንድ የበለፀገ ሀገር መሪ እጅ መላ አካላቸው በመሸፈኑ የሚሊኒየሙ ዕቅድ ተሳክቷል ለማለት ያስደፍራል። ሥጋ ባዳ ነው አሉ !!
ጠቅላይ ሚኒስተሬ ከወዴት አሉ!?
**በእርግጥ በፎቶ ላይ ካልተገኙ ወይንም ዘግይተው ከመጡ ጉዳዩ” ባለፈው በአርዓያነቱ በአቶ ሁሴን ኦባማ የተደነቀው ገበሬ ለቀዳማዊት እመቤት ሚሼል ኦባማ ለጋ የራስ ቅቤ ልኮላቸው ሽብርተኛ እንዳይረብሸው በመጠበቅ ሲሯሯጡ ነው።” ጠ/ሚ ለገሠ ግን ያዳላሉ ለቻይናው አቻቸው የተለያዩ የብሔር ብሔረሰቦችን በቁም አቅርበው አሰገዱላቸው ወይንስ(…)
አቤ ሰውየው ተገኝተዋል ሪፖርተር ላይ ወሮታውን እከፍላለሁ ባትልም አንደኛ አግኝ ስለሆንኩ ወሮታው ይገባኛል ቂቂቂቂቂቂቂ በቃ ሞትኩ በሳቅ፡፡
ኖር ወዳጄ እንዴት ከርመሃል….ሰውዬው እንደዚ ከስጋ ተራ ወደ አጥንት ተራ የገባው በአቤ ድምጽ ከሆነ የዛች ሙጢ ሚስቱ ቁንጥጫ ቢጨመርበት ከአጥንት ተራ ወዴት ያመራ ይሆን ?..***.መታደል ነው አንዳንዱ 4×8 ሆኖ በጂም አደለም በጅብም ቢበላ መቀነስ አቅቶታል ቅንድቦ በድምጽ ወደ አጥንት ተራ ዋው አፍ ብያለው ክራይም ሚንስተር ኦፍ አድዋ !!
እኔ እንደሚመስለኝ መሪያችን የኣበበን ” መለስ ኢዝ ኤ ዲክታተር” የሚል ዘለፋ ፈርተው የፎቶ ስነ ስርዓቱ እስኪፈጸም
ወደ ሽንት ቤት ጎራ ያሉ ነው የሚመስለኝ።
ሰለሞን ንካልኝ ምን ብሎ እንደ ሚነካው ጓጉቻለሁ። አሁንም በዘመኑ ቴክኖሎጂ ተጠቅመው ከሰዎቹ መካከል አጠፏቸው ይል ይሆን!!?
Michelle Obama Dances ‘The Dougie’ At Alice Deal Middle School (you tube)
*አያችሁ የሀገራችን ለጋ ቅቤ እንዴት እንደምትናጥ (ሚኒስትርህ ተገኙ) ግን ያው እንደፈራሁት “የኮመዲቲ ኤክስቼንጅ” ሃላፊ ከገበሬው ያመጡትን የራስቅቤ አስረክበው በ፸ ከመቶ ዕንባ አቅርረው ተሰናበቱ!?።
**አጎት ኦባማ በሙሉ ሱፍ ልብስ ቂቅ ብለው ካንቆለጳጰፁት ይልቅ… ኮታቸውን አውልቀው በሸሚዝ ዱቅ ብለው ያስተላለፉትን መልዕክት ገብቶአቸው በጊዜ ላጥ ማለታቸው በጣም አስገርሞኛል !!
***በዕድገት ነው? ተቀንሰው? ወይንስ ቀንሰው ( -) ?
አብየታዊ ዲሞከራሲ ፓርቲ ለወሳኝ ሕልውናው ሲል አስቸኳይ ግምገማ ከባለሥልጣን ,ደጋፊና ካድሬ ጭምር ካላደረገ የአየር ሁኔታው እጅግም ጤነኛ አደለም እና ቢዘንብም ባይዘንብም ጃንጥላችሁን አትርሱ ሲዘንብ ያብባል በለው!
ነገር ግን ተስብሳቢዎቹ ፎቶግራፍ ላይ የሉም ክሳታቸው ይሄንን ያህል እንዳይታዩ አድርጓቸው ነው ወይስ ፎቶግራፍ አንሺው እሳቸው ነበሩ!? really Abe asakegn.