ዛሬ ግንቦት ሰባትን አስመልክቶ አንዳንድ የተለቃቀሙ ጨዋታዎችን ለማቅረብ ዕቅድ ነበረኝ ነገር ግን በ”ሙድ” እጦት ጨዋታው ሳያልቅልኝ ቀኑ አለቀብኝ። ስለዚህ ለዛሬ ቢያንስ እንኳን አደረሳችሁ እንባባል። እና ለነገ በሀገርቤቱም በዲያስፖራውም ብሎጋችን “ሙድ ያፈራውን” የግንቦት ሰባት ወሬ እንቃመሳለን። (ማስታወቂያ መሆኑ ነው እንግዲህ) ኢቲቪም “በነገው ዕለት”  አያለ የፕሮግራም ማስታወቂያ ይሰራ የለ እንዴ…? ማን ከማን ያንሳል!

በነገራችን ላይ ለኢትዮጵያ ብለን የከፈትነው 15ኛው ብሎጋችን እስከ አሁን ባለመዘጋቱ የተሰማኝን መደነቅ ሳልገልፅ አላልፍም። አሁንም በነገራችን ላይ ዋናው ብሎጋችን እስከ አሁን ደረስ ከመቶ ሺህ ግዜ በላይ የተጎበኘ ሲሆን ሌሎቹ አስራ አራቱ ብሎጋ ብሎጎችም ከ ሃያ ሺህ እስከ አራት ሺህ ግዜ ድረስ ተጎብኝተው “የተሰዉ” ናቸው። “እንደምታነቡኝ ባወቅሁ ግዜ ደስ አለኝ” የሚባለው ይሄኔ ነው! የነገ ሰው ይበለን!

About abetokichaw

ራሱን አቤ ቶኪቻው እያለ የሚጠራ አንድ ግለሰብ በአዲሳባ ከተማ ይኖር ነበረ። በአዲሳባ ከተማ በሚኖርበት ግዜ የመንግስትን ያልተስተካከለ አስራር ሲያሽሟጥጥ መንግስት ተቀየመው። ምን መቀየም ብቻ… ከሀገር እንዲሰደድ ሁሉ አደረገው እንጂ! ይህ ግለሰብ… ከዚህ በፊት ሁለት ሽሙጣዊ መፅሐፍትን ያሳተመ ሲሆን “የአቤ ቶኪቻው ሽሙጦች” እና “ስላቆች” ይሰኛሉ። አሁንም ቢሆን የማይሆን ነገር ካየሁ ከማሽሟጠጥ አልመለስም የሚለው ይህ ስደተኛ… እነሆ በዚህ ብሎግ ላይ ደግሞ በሽሙጥ የአፃፃፍ ብልሃት ቢያንስ በሳምንት አንድ ግዜ ልከሰት ብሎ “ሀ” ብሏል።

Leave a Reply

Fill in your details below or click an icon to log in:

WordPress.com Logo

You are commenting using your WordPress.com account. Log Out /  Change )

Facebook photo

You are commenting using your Facebook account. Log Out /  Change )

Connecting to %s