ፕሮፌሰር መስፍን ወልደማሪያምን ሚያዝያ 16 ቀን 2004 ዓ.ም የልደት በዓላቸው ነበር። ይህንኑ አስመልክቶ ዛሬ በርካታ ወጣቶች ቤታቸው ድረስ ሄደው ልደታቸውን አክብረውላቸዋል። (በቅንፍም ታድያ ባዶ እጃቸውን አይደለም የተለያዩ ስጦታዎችን ይዘውላቸው እንጂ! ብዬ እጨምራለሁ።) በፕሮግራሙ ላይ ከተገኙት እና ለፕሮፌሰር መስፍን የአክብሮት ስጦታ ካበረከቱ ወጣቶች መካከል ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ አንዱ ነበር!
እኔም ብኖር ኖሮ አልቀርም። እናም አምልጦኛል። ቢሆንም ግን በዝች መልዕክት ማስተላለፊያ ፕሮፍ እንኳን አደረስዎ በቀጣይም ረጅም እድሜን እመኝልዎታለሁ! ለማለት እወዳለሁ።፡
ቀጥሎ ከጋሽ ፍቅሩ ኪዳኔ “ፒያሳ” መፅሐፍ ውስጥ የሚከተለውን እንድናነብ እጋብዛለሁ፤ ትንሽ ለመንደርደር ከየት እንጀምር…. አዎ…
“… በ1950 የስዊዲኑ ኖርቺፒንግ ቡድን ለሶስት ግጥሚያዎች መጥቶ ሲጫወት ያሁኑ ስታድየም ገና በመሰራት ላይ መሆኑን አስታውሳለሁ። በባዶ እግራቸው ይጫወቱ የነበሩት ጫማ በልካቸው ፒያሳ እያሰፉ መጫወት ጀመሩ።
የኛ ጫማ ሰፊዎች የፈረንጁን ሞዴል እያዩ የሚሰሩ ቀልጣፎች መሆናቸው ተመስክሮላቸዋል። ለመለካትም ሆነ ፕሮቫ ለማድረግ የሚሄደውን ቡና ወይም ሻይ መጋበዝ ተለምዷል። የብስክሌት ተወዳዳሪ የነበረው አቶ አበበ ማሞ ጥሩ ጫማ ሰፊ ነበር። የአስመራና የድሬደዋ ቡድኖች በኢትዮጵያ ሻምፒዮና መካፈል በመጀመራቸው የፉትቦል ጨዋታው ተስፋፋ። ከጥንት ጀምሮ የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ብዙ ቀልጣፋ ተጫዋቾች ስለነበራቸው ለልዩ ልዩ ክለቦች ይጫወታሉ።
በዚያን ግዜ በነ ጌታቸው መድህኔ፣ መስፍን ወልደማርያም፣ ኃይሉ አፈወርቅ፣ ልዑል ሰገድ በቀለ፣ ንጉሴ ፍትአወቅ፣ እልፍአግድ ጎበና፣ ፀጋዬ በቀለ፣ ዘውዴ ሳሙኤል እና ሌሎችም የነበሩበት የተፈሪ መኮንን ት/ቤት ቡድን የጦር ሰራዊትን ቡድን አሸንፏል። ወዳጄ ፕሮፌሰር መስፍን ወለወደማርያም በተከላካይ ስፍራ ይጫወት ስለነበር አሁንም የመከላከል ተግባሩን ቀጥሏል። ምንም አንኳ አርቢተሩ ቀይ ካርድ እያሳየ ቃሊቲ ቢከተውም፣ ለኢትዮጵያ ብሔራዊ ፖለቲካ ቡድን መጫወቱን አላቋረጠም።”
ጋሽ ፍቅሩን እያመሰገንን ፕሮፌሰር መስፍን በቀጣይም ለኢትዮጵያ ብሔራዊ ፖለቲካ ቡድን በተከላካይ ስፍራ እየተጫወቱ እንከኖቻችንን ይከላከሉልን ዘንድ በድጋሚ ረዥም ዕድሜ ይስጥልን ብለን እንመርቃለን!
በመጨረሻም
“አደጋ ያንዣበበበት የአፍሪካ ቀንድ” የተሰኘው የፕሮፌሰር መስፍን መፅሀፍ ደርሶኛል። ላኪዎቼም አድራሾቼም እግዜር ይስጥልኝ አሁን ቶሎ ብዬ እርሱን ማንበብ አለብኝ!
abe- i like ur new website color and features.
keep it up
Good Job, Abe..:)
Thanks, God bless you!!!
ምን ለመሆን ነው ረጅም እድሜ የተመኘህላቸው አቤ ለ50 አመታት ግድም የቋመጥዋትን የምንልክ ወንበር መቸም ከአሁን ብኋላ አያገኝዋትም ያው ወደ ማየቀረው አለም ሲሻገሩግን በምድር ውሰጥ ምኞታቸው(ፍላጎታቸውን)ካላሰኩ ሰዎች ስም ዘርዝር ውሰጥ ይመዘገባሉ ብየ ተስፈ አደርጋሎ
Melkam ledet !! neger gin min yahel le Ethiopia min seru? sentunse asaku? ahunse min eyseru new??? tenan ena edeme yestachew!!