የፍትህ ጋዜጣ ዋና አዘጋጅ ተመስገን ደሳለኝ በእነ አንዷለም አራጌ የክስ መዝገብ የተከሰሱ ሰዎችን ቃል በጋዜጣህ ላይ አትመሃል ይህም በፍርድ ሂደቱ ጣልቃ መግባት ነው ተብሎ ተከሶ እንደነበር ይታወቃል። (ካልታወቀም አሁን ይታወቅ… ልል ነበር በዜና ላይ አይቀለድም ለካ…)

ተሜ የተከሰሰበት ጣልቃ መግባት ክስ የአንዷለም አራጌን፣ የእስክንድር ነጋ፣ የናትናኤልን እና የአበበ ቀስቶን ፅሁፍ በጋዜጣህ ላይ በማተምህ የሚል ሲሆን፤ ተመስገንም “ተጠቃሾቹ የሰጡኝን ፅሁፍ የማተም መብት አለኝ” ሲል ተከራክሮ ነበር።

በዚህም ምክንያት “እውነትም ተጠርጣሪዎቹ ፅሁፉን ሰጥተውት ነበር ወይ?” የሚለውን ለማጣራት ለእማኝነት የተጠራው አበበ ቀስቶ… “ፅሁፉ የኔ ነው በወጣው ነገር መጠየቅ ካለብኝ የምጠየቀው እኔ ነኝ እንጂ ተመስገን አይደለም። በጋዜጣው ላይ የታተመው በፍርድ ቤት ላቀርበው እፈልግ የነበረ ሃሳብ ነው። ነገር ግን ፍርድ ቤቱ ግዜ ሊሰጠኝ ስላልቻለ እንዲታተም ሰጥቼዋለሁ…” ብሎ ሲናገር ዳኛው “ንግግርህን አሳጥር ይህንን የጠየቀህ የለም” በማለት አቋርጠውታል።

በዛሬው የተመስገን ደሳለኝ ችሎት ካለፉት ግዚያት የበለጠ በርካታ ሰው ተገኝቶ እንደነበር ከስፍራው የደረሰኝ ወሬ ያስረዳል።

ፍርድ ቤቱ የምስክሩን ክንፈ ሚካኤል ደበበ (አበበ ቀስቶ) ቃል ከሰማ በኋላ ለሚያዝያ 22 ቀጠሮ ሰጥቶ ተበትኗል።

በነገራችን ላይ ሚያዝያ 24 ኢቲቪም በአኪልዳማ የተነሳ ፍርድ ቤት እንደሚቆም ባለፈው ተጨዋውተናል አይደል። እስቲ የሚባለውን እንጠብቃለን!

About abetokichaw

ራሱን አቤ ቶኪቻው እያለ የሚጠራ አንድ ግለሰብ በአዲሳባ ከተማ ይኖር ነበረ። በአዲሳባ ከተማ በሚኖርበት ግዜ የመንግስትን ያልተስተካከለ አስራር ሲያሽሟጥጥ መንግስት ተቀየመው። ምን መቀየም ብቻ… ከሀገር እንዲሰደድ ሁሉ አደረገው እንጂ! ይህ ግለሰብ… ከዚህ በፊት ሁለት ሽሙጣዊ መፅሐፍትን ያሳተመ ሲሆን “የአቤ ቶኪቻው ሽሙጦች” እና “ስላቆች” ይሰኛሉ። አሁንም ቢሆን የማይሆን ነገር ካየሁ ከማሽሟጠጥ አልመለስም የሚለው ይህ ስደተኛ… እነሆ በዚህ ብሎግ ላይ ደግሞ በሽሙጥ የአፃፃፍ ብልሃት ቢያንስ በሳምንት አንድ ግዜ ልከሰት ብሎ “ሀ” ብሏል።

Leave a Reply

Fill in your details below or click an icon to log in:

WordPress.com Logo

You are commenting using your WordPress.com account. Log Out /  Change )

Facebook photo

You are commenting using your Facebook account. Log Out /  Change )

Connecting to %s