ኢናሳ የተባለው የኢትዮጵያ ቆላፊ እና ጠላፊ መስሪያ ቤት የግለሰቦችን ፌስ ቡክ ሳይቀር በመቆለፍ ስራ ተጠምዷል። በትላንትናው ዕለት በርካታ ብሎጎች ድጋሚ እንደተዘጉ ሰምተናል። መንግስቴ ፈርቷል… በእውኑ እንዲህ ያለው ፍርሃት “ተራሮችን ካንቀጠቀጠ ትውልድ” አይጠበቅም…
እኔን ጨምሮ ሌሎችም “ባለ ብሎጎች” አንዱ ቢዘጋ በሌላ መስኮት ወደ አገራቸን መግባታችን እና ከወዳጆቻችን ጋር መጨዋወታችን እንደሚቀጥል እርግጠኛ ነኝ። ስለዚህ የተዘጋው በር ሁሌም መንኳኳቱ አይቀርም ማለት ነው። ታድያ በተንኳኳ ቁጥር መንግስት እየተነሳ ሲዘጋ መንግስቴን ስትራፖ እንዳይዘው ሰጋሁለት…!
የዛሬ ሃሳቤን በግጥም ብገልፅ በደንብ ይወጣልኝ ነበር። ነገር ግን ብንደፋደፍ ብንደፋደፍ ጠብ ሊልኝ አልቻለም። ታድያ ከወዳጆቼ ጋር ለምን አናዋጣም ብዬ እንደዚህ ጀመርኩ፤
በአንኳኪ ብዛት ሰላም ከምታጣ
በርህን ክፈተው ያሻው ይግባ ይውጣ…
ይበሉ ወዳጄ አንድ አንድ ስንኝ ያዋጡ… ከዛ ዜማ አበጅተን እንዘፍናት ይሆናል።
አልከፍተውም ብለህ ዘግተህ ከተቀመጥክ
ሁሌም ስናንኳኳ ሰላምክን ታጣለክ…..
ቁልፎቹ ላይ ቆመህ በፋራ ረገጣ
“በመስኮት ዝለሉ” ካልከን በለገጣ
ልናርፍ እንችላለን ከራስህ መላጣ
በአንኳኪ ብዛት ሰላም ከምታጣ
በርህን ክፈተው ያሻው ይግባ ይውጣ
ብየ ባማክረው የእቴጌዋን ባል
አንት አሸባሪ እስር ይገባሃል
ብሎ መለሰልኝ ፍርድን ቀለል አድርጎ
ቀጥሉበት …..
ማሪያምን ብያለሁ ክፈተው በሩን
ደምም ሳንፋሰስ ሳልመዘው ጦሬን፤
በጣም ተከፍቼ ብሶቴን ሳሰማ
ጆሮ ዳባ ካልከኝ ምንም እንዳልሰማ፤
ቤቴ የገባሁ ቀን…፣ ቤቴ የገባሁ እለት!!!
በጦሬ በጥሼ የበሩን ሰንስለት
አንተን አያድርገኝ አቤ..ት ያችን ሰዐት።
great one
thanks ermi
በመረጃው ዘመን ዓለም አንድ ሆና
ካንዱ ጫፍ አንዱ ጫፍ በሰኮንዶች ፍጥነት እያገኘን ዜና
ያለም ሳይንቲስቶች፤ ጠቢባን ጉድ በሉ
ጦቢያ በብረት ቁልፍ ተዘግታለች አሉ።
ልጆቿ አለቀሱ፣እራበን እያሉ፥
የንጀራው ሲገርመን መረጃም ተራቡ፣
ያለም ሃገራትን እድገት ነፃ አዋጣ፥
ከድህነት ማዕበል ከልመና ጣጣ
ነገር ተገልብጦ እሱስ በኢትዮጵያ አሳር ይዞ መጣ፥
እንጀራ እየቀጣ ሰው ዜና እያሳጣ።
የበሩ ዘበኛ አንተ ቆላፊው
ከማንስ አይተህ ነው፥
ከየት ተማርከው።
ማርክም በፌስቡኩ ዓለምን አንድ ሲያረግ፥
አንተ እንደ ግመል ሽንት ወደኋላ ወረድክ።
አሁንም ልምከርህ፥
ጊዜው ሳይረፍድብህ
ለቅዘን ያለው ቂጥ ምንግዜም ላይጠራ
በአንኳኪ ብዛት ሰላም ከምታጣ
በርህን ክፈተው ያሻው ይግባ ይውጣ…
ኢናሳ የኢትዮጵያ ቆላፊ፤ መረጃ ጠላፊ አስጠላፊ፤ ቀበኛ የጓዳ አይጥ ቀፋፊ ፤ ቀንህ ደርሶ ሳትመታ በጥፊ ፤ ክፈት ብለናል በሩን ፤ የሕዝቡን ልሳን የዘጋኸውን ፤ አቁም ፍራቻን መደናበርክን፤ መርጠን እኮ ነው መከባበሩን፤ መች ጠፋን እና ሰበሮ መገባትን፤ ያሻው ይውጣ ይግባ ይተያይ ፊቱን፤ ቁልፍ እና ሰነሰለት የማይበግረን፤ ሲንኳኳ ተሸበርክ እንኳንም ከፍተን፤ ልብ ካለህ ክፈትና ግጠመን፤ ሰሚ ብናገኝ ተው በለው! አልን።
ኢናሳ የኢትዮጵያ ቆላፊ፤ መረጃ ጠላፊ አስጠላፊ፤ ቀበኛ የጓዳ አይጥ ቀፋፊ ፤ ቀንህ ደርሶ ሳትመታ በጥፊ ፤ ክፈት ብለናል በሩን ፤ የሕዝቡን ልሳን የዘጋኸውን ፤ አቁም ፍራቻን መደናበርክን፤ መርጠን እኮ ነው መከባበሩን፤ መች ጠፋን እና ሰበሮ መገባትን፤ ያሻው ይውጣ ይግባ ይተያይ ፊቱን፤ ቁልፍ እና ሰነሰለት የማይበግረን፤ ሲንኳኳ ተሸበርክ እንኳንም ከፍተን፤ ልብ ካለህ ክፈትና ግጠመን፤ ሰሚ ብናገኝ ተው በለው! አልን።
መንግሥት ቤቱን ዝግቶ ብቻውን ይብላል
አበው ተናግረዋል ብቻዉን ይሞታል
እኔስ እገባልሁ በተገኘው ቦታ አሁንስ ይበርግግ ሲሰማ ኮሽታ