ብሎጋችን ላለፈው አንድ ሳምንት ወደ ኢትዮጵያ እንዳትገባ ታሽጋ ሰንብታ ዛሬ ድጋሚ “ግድየለም ትግባ’ ተብሎ ተፈቅዶላታል። በርካታ ወዳጆቼ ከኢትዮጵያ ሆነው እንዳነበቡኝ በስታስቲክሱ ላይ ባየሁ ግዜም ገቡ ገቡ ገቡ! ብያለሁ።

ባለፈው ግዜ ወዳጃችን ተመስገን ደሳለኝ የፍትህ ዌብሳይት የተዘጋ ግዜ “በህግ አምላክ” ብሎ ሲያበቃ ሲከፈት ደግሞ ምስጋና ማቅረብ ተገቢ አለመሆኑን ተናግሮ ነበር። እኔም ዘጊዎቹንም ከፋቾቹንም ለማመስገን እንደማልወድ ለማሳወቅ እፈልጋለሁ።

ቀድሞውንም ከወዳጆቼ ጋር የሆድ የሆዴን ልጫወት የከፈትኩትን ብሎግ መዝጋት አግባብ አልነበረም።

እውነቱን እንነጋገር ከተባለ ብሎግን መገደብ የኤሌክትሪክ ሃይል አያመነጭም። እናም እባካችሁን ቀጥሎም አትገድቡን እናውጋበት… እንዋጋ አላልኩም!!!

ውድ የብሎጌ ታዳሚዎች እንግዲህ ባመቻችሁ መስኮት እየገባችሁ እንገናኛለን ማለት ነው!

About abetokichaw

ራሱን አቤ ቶኪቻው እያለ የሚጠራ አንድ ግለሰብ በአዲሳባ ከተማ ይኖር ነበረ። በአዲሳባ ከተማ በሚኖርበት ግዜ የመንግስትን ያልተስተካከለ አስራር ሲያሽሟጥጥ መንግስት ተቀየመው። ምን መቀየም ብቻ… ከሀገር እንዲሰደድ ሁሉ አደረገው እንጂ! ይህ ግለሰብ… ከዚህ በፊት ሁለት ሽሙጣዊ መፅሐፍትን ያሳተመ ሲሆን “የአቤ ቶኪቻው ሽሙጦች” እና “ስላቆች” ይሰኛሉ። አሁንም ቢሆን የማይሆን ነገር ካየሁ ከማሽሟጠጥ አልመለስም የሚለው ይህ ስደተኛ… እነሆ በዚህ ብሎግ ላይ ደግሞ በሽሙጥ የአፃፃፍ ብልሃት ቢያንስ በሳምንት አንድ ግዜ ልከሰት ብሎ “ሀ” ብሏል።

5 responses »

  1. እንዲያው ቢጨንቃቸው ነው እንደዚ የሚዙትን የሚጥሉትን ያሳጣቸው !!!

  2. Addis says:

    ወደዱም ጠሉ እኛ እና አንተን ለማራራቅ የሚደረገው ሴራ መቼም አይሆንም በልልኝ ለነዚያ ጬኒዎች ላስተካክለው ተአይነ ጠባቦቹ ቻይኖች

  3. Bele says:

    yelijoch dibibikosh chewata eyetechawotu new. des yilal yehager astedadariwoch honew sayikuraru yihen chewata sichawot

  4. Berta Abe says:

    Abe nebse… Liben eko new yemitarisegn!!! I love you man!

  5. rediet says:

    abe nebs neger…..yimecheh abo

Leave a Reply

Fill in your details below or click an icon to log in:

WordPress.com Logo

You are commenting using your WordPress.com account. Log Out /  Change )

Facebook photo

You are commenting using your Facebook account. Log Out /  Change )

Connecting to %s